በግብዓት አቅርቦት ፓሊሲ፣ ስትራቴጅዎች እና ሌሎች ሰነዶች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ

11/03/2025

Financial and Audit Report 2020/21

28/01/2025

ማስታወቂያ

25/10/2023

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ የበላይ አመራሮች ከኢኢግልድ አመራሮች ጋር ውይይትና የስራ ጉብኝት አካሄዱ

26/12/2024

የኢኢግልድ የበላይ አመራሮችና ሃላፊዎች በግንባታ ላይ የሚገኘውን ዋና መ/ቤት ህንፃ ጎበኙ

02/12/2024

ኢኢግልድ በበጀት ዓመቱ አራት ወራት የዕቅዱን 96 በመቶ ማከናወኑ ተገለጸ

23/10/2024

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅትና የኢትዮጵያ ፖስታ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ሠነድ ተፈራረሙ

23/10/2024

በኢንዱስትሪ ግብዓቶች አቅርቦት ተግዳሮቶችና መፍትሄ ላይ ውይይት ተካሄደ

14/10/2024

እንኳን ደስ አላችሁ!!!

11/10/2024

ኢኢግልድ ላገኘው የ2016 በጀት ዓመት ስኬታማ አፈጻጸም ለአመራሮቹና ሠራተኞቹ እውቅና ሰጠ

26/08/2024

ኢኢግልድ የአቢሲኒያ ኢንዱስትሪዎች ሽልማት ከፍተኛ ተሸላሚ ሆነ

22/07/2024

የመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታ አስተዳደርና ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሃላፊዎች የችግኝ ተከላ አካሄዱ

20/07/2024

የማዕከላዊና የምዕራብ ዲስትሪክት ጽ/ቤቶች አስር ወራት ዕቅድ አፈጻጸምና 2017 የኮርፖሬት ዕቅድ ግምገማ ተካሄደ

20/05/2024

ኢኢግልድ በስትራቴጂክ ዕቅዱና በአሰራር መመሪያዎች ረቂቅ ላይ ሲያካሂድ የነበረውን ግምገማ አጠናቀቀ

13/05/2024

ኢኢግልድ ስትራቴጂክ ዕቅዱና ሌሎችም የአሰራር ስርዓቶቹን እየገመገመ ይገኛል

10/05/2024

ኢኢግልድ በኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ላይ ተሳተፈ

09/05/2024

ኢኢግልድ 10ኛው አገር ዓቀፍ የሕብረት ሥራ ማሕበራት ኤግዚቢሽንና ባዛር ተሳተፈ

15/02/2024

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ኢንዱስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት በኢኢግልድ ጉብኝት አካሄዱ

29/01/2024

የአመራሮችና የባለሙያዎች ቅንጅትና የስራ ትጋት ለድርጅቱን አፈጻጸም ውጤታማነት ሚና እንደሚኖረው ተገለጸ

17/01/2024

ማስታወቂያ

27/11/2023

— 20 Items per Page
Showing 1 - 20 of 50 results.

በግብዓት አቅርቦት ፓሊሲ፣ ስትራቴጅዎች እና ሌሎች ሰነዶች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት(ኢኢግልድ) ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ጋር በመቀናጀት በኢንዱስትሪ ግብዓቶች አቅርቦት ጋር በተያያዘ የአምራች ኢንዱሰትሪውን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ በተዘጋጀ ፖሊሲ፣ በተቀረፁ የተለያዩ ጥናቶችና ስትራቴጂዎች ላይ ከየካቲት 25 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለሁለት ቀናት በቢሾፍቱ ከተማ ለኢኢግልድ ከፍተኛ አመራሮች፣ ከተለያየ ክፍል ለተውጣጡ ዳይሬክተሮች፣ የዲሰተሪክት ሃላፊዎችና ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ፡፡

በስልጠናው የኢኢግልድ ዋና ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ የሺመቤት ነጋሽ የመክፈቻ ንግግር በማድረግ ስልጠናውን ያስጀመሩ ሲሆን የስልጠናው ዋና ዓላማ ኢኢግልድ ከኢንዱስትሪዎች ፍላጎት አንጻር የግብዓት አቅርቦት ስራ ሂደቱን ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ስትራቴጂ ጋር የተናበበና የተቀናጀ በማድረግ ለመስራት እና የግብዓት አቅርቦት ሰንሰለቱን የተሳለጠ በማድረግ በቀጣይ ውጤታማ ስራ ለመስራት እንዲያስቻል ታስቦ የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን አመልክተዋል፡፡

ለሁለት ቀናት በተካሄደው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና የተለያዩ ስትራቴጂዎችና ጥናቶች የቀረቡ ሲሆን የኢትዮጲያ የኢንዱስትሪ ፖሊሲ፣ የተኪ ምርት ስትራቴጂ፤ የአምራች ኢንዱስትሪ የትስስር ስትራቴጅ ሰነድ የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ የኤክስፖርት ስትራቴጂ፣ የቆዳ ስትራቴጂና የማስፈጸሚያ ስልት እንዲሁም የጥጥ ግብይት ስርዓት ጥናቶች ለስልጠናው ተሳታፊዎች ቀርበዋል፡፡ በቀረቡት ሰነድ ላይም የስልጠናው ተሳታፊዎች ከኢኢግልድ አንፃር ጥያቄዎችን እና አስተያየቶችን በማቅረብ ሰፋ ያለ ውይይት በኢንዱሰትሪ ሚኒሰቴር የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ዋና ዳይሬክተር በሆኑት ዶ/ር ሚልኬሳ ጃግሜ እና በአሰልጣኞች አወያይነት ተካሂዷል፡፡

በመጨረሻም የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሚልኬሳ ጃግሜ በስልጠናውና የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሐግብር ማጠናቀቂያ ላይ እንደገለጹት የዚህ ዓይነት የስልጠና መድረክ በኢንዱስትሪ ግብዓት አቅርቦት ዘርፍ ዋና ባለድርሻ ለሆኑት የኢኢግልድ ከፍተኛ፣ መካከለኛ አመራሮችና ባለሙያዎች መዘጋጀቱ የኢንዱስትሪ ግብዓት አቅርቦት ሰንሰለቱን የተሳለጠ እንደሚያደርገው አመልክተው፤ የዚህ ዓይነት ይዘት ያላቸው የተለያዩ ነገር ግን የአንድ ዓላማ ግብን ለማሳከት የሚያስችሉ፤ ተቋማትን የሚያስተሳስሩ ስትራቴጂዎችና ጥናቶች ላይ የጋራ ግንዛቤ መያዝ በእጅጉ አስፈላጊ በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል፡፡